በኩር ማክሰኞ መጋቢት 15 ቀን 2018ዓ.ም
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የሁለት እጅ
እነሴ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ግዥ ቡድን በወረዳው ውስጥ ላሉት መኪኖች አገልግሎት የሚውል የመኪና ጐማ ከነ ካለመዳሪው፣ የመኪና
መለዋወጫ፣ ለእንሰሳት ጽ/ቤት አገልግሎት የሚውል የእንሰሳት መድሃኒት፣ ባቱስ ጽ/ቤት አገልግሎት የሚውል የስፖርት ትጥቅ፣ ለተለያዩ
ሴክተር መ/ቤቶች አገልግሎት የሚውል የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች፣ ለተለያዩ ሴክተር መ/ቤቶች አገልግሎት የሚውል ፈርኒቸር፣ በወረዳው
ውስጥ ላሉ የፑል መ/ቤቶች አገልግሎት የሚውል የጽዳት እቃዎች፣ የየጭቃ ጤና ጣቢያ ተቋርጦ የቆየ ደረጃ ማሳደግ ግንባታ በግልጽ
ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት (ለማሰራት) ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ይችላሉ፡፡
1 በዘመኑ
የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
2 የግብር
ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ማቅረብ የሚችሉ፡፡
3 የግዥው
መጠን ብር 200,000 (ሁለት መቶ ሺህ ብር) በላይ ከሆነ የተጨማሪ ዕሴት ታክስ (ቫት) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ
የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
4 ተጫራቾች
በጨረታው ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር 1-3 የተጠቀሱትን እና የሚመለከታቸው ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው
ማቅረብ ግዴታ አለባቸው፡፡
5 የጨረታ
ሰነዱ ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፊኬሽን) ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
6 ተጫራቾች
የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 200 (ሁለት መቶ ብር) ለሁሉም ግዥዎች ለእያንዳንዳቸው ሰነድ እና ለየጭቃ ጤና ጣቢያ ግንባታ
ብር 500 (አምስት መቶ ብር) በመክፈል ከሁ/እ/እ/ወ/ ገንዘብ ጽ/ቤት ከረዳት ገ/ያዥ ቢሮ ማግኘት ይችላሉ፡፡
7 ተጫራቾች
የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) ለሚወዳደሩበት የሞሉትን ጥቅል ዋጋ ለመኪና መለዋወጫ ብር 30,000 (ሰላሣ ሽህ ብር)፣
ለመኪና ጐማ ከነካለመዳሪው ብር 40,000 (አርባ ሽህ ብር)፣ ለእንሰሳት መድሀኒት ብር 20,000 (ሀያ ሽህ ብር)፣ ለባቱስ
ጽ/ቤት የስፖርት ትጥቅ ብር 30,000 (ሰላሣ ሽህ ብር)፣ ለኤሌክትሮኒክስ እቃዎች ብር 50,000 (አምሣ ሽህ ብር)፣ ለፈርኒቸር
እቃዎች ብር 30,000 (ሰላሣ ሽህ ብር)፣ ለጽዳት እቃዎች 80,000 (ሰማንያ ሽህ ብር) ለግንባታው እንዲሁም ብር 100,000
(አንድ መቶ ሽህ ብር) በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ
ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው፡፡ በጥሬ ገንዘብ የሚያስይዙ ገንዘቡ በሁ/እ/እ/ወ/ ገንዘብ ጽ/ ቤት የገቢ ደረሰኝ ገቢ መደረግ አለበት፡፡
8 አሸናፊው
ተጫራች የውል ስምምነት እንዲፈፀም በተገለፀበት ጊዜ ውስጥ ከአሸነፈበት የዕቃ አገልግሎት ጠቅላላ ዋጋ 10 በመቶ የተሽከርካሪ ኩንትራት
ጥገና ከሆነ 3 በመቶ የግዥ ውል ማስከበሪያ ፐሮፎርማንስ ቦንድ በታወቀ ባንክ በተረጋገጠ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በጥሬ ገንዘብ
ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና /unconditional bank grante/ ማስያዝ ይኖርበታል፡፡ ከአሸናፊው የሚቀርበው
የውል ማስከበሪያ ዋስትና ጸንቶ መቆያ ጊዜ ውሉ ከሚጠናቀቅበት የመጨረሻ ቀን በኋላ ቢያንስ ለተጨማሪ 30 ቀናት ጸንቶ መቆየት ይኖርበታል፡፡
9 ለግንባታ
ስራ አሸናፊ ግንባታውን ያሸነፈበት ጠቅላላ ዋጋ 25 በመቶ ከማህንዲሱ ግምት ዝቅ ብሎ ካሞላ
-Cost breakdown
እና projeket work schedule እንዲሁም በሞላው ዝቅተኛ ዋጋ መስራት የሚችል መሆኑን የሚያረጋግጥ ደብዳቤ /conformation
letter አሸናፊነት ከተገለጸ በ5 የስራ ቀናት ውስጥ ማቅረብ አለበት፡፡ የተጋነነ ዝቅተኛ ሞልተው አሸናፊ ሆነው የግንባታ ተቋራጭ
ውል ይዘው ወደ ስራ ሲገቡ ቅድመ ክፍያ አይፈቀድላቸውም፡፡
-የውል ማስከበሪያ
የሞላውን ጠቅላላ ዋጋ 10 በመቶ የነበረው ተሻሽሎ 25 በመቶ የውል ማስከበሪያ ዋስትና ማስያዝ ግዴታ ይሆናል፡፡
10 የግንባታ
የሂሳብ ስሌት በተመለከተ አርቴሜቲክ ቸክ/ በግዥ ፈጻሚ መ/ቤት ባለሙያ ከሚያስተካክለው ውጭ በተጫራቾች በሚቀርበው በተጫራቾች በሚቀርበው
የመጫረቻ ሰነድ ላይ በነጠላ እና በጠቅላላ ዋጋ ላይ ሥርዝ ድልዝ ካለ ተጫራቹ ከጨረታ ውጭ ይሆናል፡፡
11 ለግንባታ
ለፋይናስ ግምግማ ያለፉ ተጫራቾች ቢያንስ 3 እና በላይ ከሆኑ በጨረታ አከፋፈት ወቅት ከተነበበው አጠቃላይ ዋጋ ላይ ከሂሳብ ስሌት
አርቴሚቲክ ቸክ ከተሰራ በኋላ የተደረሰበት ልዩነት እስከ5 በመቶ ድረስ ከሆነ ተቀባይነት የሚኖረው ሲሆን ከዚህ የበለጠ ልዩነት
ካጋጠመ ከውድድር ውጭ ይሆናሉ፡፡ ተጫራቾች ከ3 በታች ከሆነ በጨረታ አከፋፈት ወቅት ከተነበበው አጠቃላይ ዋጋ ላይ የሂሳብ ስሌት
አርቲሜቲክ ቸክ ከተሰራ በኀላ የተደረሰበት ልዩነት እስከ አንድ በመቶ ድረስ ብቻ ተቀባይነት የሚኖረው ሲሆን ከዚህ በላይ ከሆነ
ከውድድር ውጭ ይሆናሉ፡፡
12 ማንኛውም
ተጫራች ሃሳቡን በአንድ ወይም አንድ ውጥ በሆኑ ሁለት ቅጅዎች ማለትም ዋና እና ቅጅ በማለት ኦርጅናል ለብቻው ቅጅውን ለብቻ በጥንቃቄ
በታሸገ ፖስታ ሁለት እጁ እነሴ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ግዥ ቡድን ወይም ቢሮ ቁጥር 4 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በሥራ ሰዓት
ጋዜጣው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለግንባታ ሥራዎች ለ21 ተከታታይ ቀናት እስከ 22ኛው ቀን 3፡30 ድረስ ማስገባት ይችላሉ፡፡ ለሌሎች
ግዥዎች ለ15 ተከታታይ ቀናት እስከ 16ኛው ቀን 3፡30 ድረስ ማስገባት ይችላሉ፡፡ (ተጫራቾች የጨረታ መወዳዳሪያ ሃሳባቸውን ዋና
እና ቅጅ ወይም ኦርጅናል እና ኮፒ ማስገባት ለመ/ቤቱ እና ለተጫራቾች ደህንነት እንጅ እንደመወዳሪያ መስፈርት አይሆንም፡፡
13 ጨረታው
ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግዥ ክፍል በቢሮ ቁጥር 4 የጨረታ ጋዜጣው በወጣ ለግንባታ ሥራዎች ለ21 ተከታታይ
ቀናት እስከ 22ኛው ቀን 3፡30 ታሽጐ በ4፡00 ይከፈታል፡፡ ለሌሎች ግዥዎች 16 ተኛው ቀን 3፡30 ታሽጐ በ4፡00 ይከፈታል፡፡
የስራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀናት ይከፈታል፡፡ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተጠቀሰው የጨረታ መክፈቻ ሰዓት ባይገኙ
መ/ቤቱ ጨረታውን የመክፈት መብት አለው፡፡
14 መ/ቤቱ
የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
15 ተጫራቾች
የሚያቀርቡት ዋጋ ማንኛውንም አይነት ግብር የሸፈነ መሆን አለበት፡፡
16 ውድድሩ
በሎት ስለሆነ በጨረታ ሰነዱ የተጠቀሱትን ሁሉንም ዝርዝሮች በሙሉ መሙላት አለባችሁ፡፡
17 አሸናፊው
ድርጅት ያሸነፋቸውን ዕቃዎች በሙሉ በራሱ ወጭ ሁለት እጁ እነሴ ወረዳ ሥር ባሉ ንብረት ክፍል ገቢ ሊያደርግ የሚችል፡፡
18 መ/ቤቱ
የሚገዛውን እቃ 20 በመቶ የመጨመር ወይም የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
19 አሸናፊው
ውል ከያዘበት ቀን ጀምሮ በሚታሰብ ሁሉንም ግዥዎች በ15 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ያሸነፋቸውን እቃዎች ሙሉ በሙሉ አጠቃሎ ማቅረብ
የሚችል ሲሆን ለየጭቃ ግንባታ ግንባታውን አጠናቆ የሚያስረክብበት ጊዜ 180 ቀናት ውስጥ መሆን አለበት፡፡
20 ለግንባታ
በጨረታው የሚሣተፋ ተጫራቾች ህንጻ ስራ ተቋራጭ እና ጠቅላላ ስራ ተቋራጭ ሆኖ ደረጃ 7 እና በላይ መሆን አለባቸው፡፡
21 በተጨማሪ
በግዥ አፈፃፀም መመሪያ ቁጥር 1/2003 እና በተሻሻለው የግንባታ አፈጻጸም መመሪያ መሰረት ተፈፃሚ ይሆናሉ፡፡
22 ስለጨረታው
ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 4 ድረስ በአካል በመገኘ ወይም በስልክ ቁጥር 058 661 00 05 በመደወል መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡
የሁለት እጅ እነሴ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት