አዲስ ዘመን እሁድ ጥቅምት 16 ቀን 2018ዓ.ም
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር፡- 01/2018
በአብክመ በምስራቅ ጎጃም ዞን የአነደድ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት በወረዳው ውስጥ ለሚገኙ
ባለበጀት መ/ቤቶች ለተለያዩ አገልግሎት የሚውሉ ሎት 1 የተለያዩ የጽ/መሳሪያዎች በጀት፣ ሎት 2 የተለያዩ የጽዳት እቃዎች፣ ሎት
3 የድምጽና ምስል እቃዎች፣ ሎት 4 ኮምፒውተርና ተዛማጅ እቃዎች፣ ሎት 5 የተለያዩ ህትመቶች፣ ሎት 6 የስፖርት እቃዎችና መገልገያዎች፣
ሎት 7 የእህል ምርት ውጤቶች እስከ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ የኮንትራት ውል አቅርቦት፣ ሎት 8 የምግብ ምርቶች
እስከ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ የኮንትራት ውል አቅርቦት፣ ሎት 9 አትክልትና ፍራፍሬ እስከ ሰኔ 30 ቀን 2018
ዓ.ም ድረስ የሚቆይ የኮንትራት ውል አቅርቦት፣ ሎት 10 የመኪና ጎማ፣ ሎት 11 የውሃ ግንባታ እቃዎች፣ ሎት 12 የስፖርት ማሊያ
በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል:: ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የሚችሉ መሆኑን ይጋብዛል::
1. በዘመኑ የታደስ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ፤ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /ቲን ነምበር/ ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፤
2. የግዥ መጠኑ ከብር 200,000.00 /ሁለት መቶ ሺህ ብር/ በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ /
የቫት ከፋይነት/ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው::
3. ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር 1-2 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ
ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው::
4. የሚገዛውን እቃ ዝርዝር መግለጫ /ስፔስፊኬሽን/ ከመጫረቻ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ::
5. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ለእያንዳንዱ ሎት ብር 100.00 /አንድ መቶ ብር/ በጥሬ ገንዘብ ወይም
በባንክ ገቢ በማድረግ ሰነዱን መግዛት ይችላል::
6. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ቢድ ቦንድ ለሚወዳደሩበት ጥቅል ዋጋ ለሎት 1 - 7,000.00
/ሰባት ሺህ ብር/፣ ለሎት2. ብር 1500.00 /አንድ ሺህ አምስት መቶ ብር/፣ ለሎት 3 - 5,000.00 /አምስት ሺህ ብር/፣
ለሎት 4-10,000.00 /አስር ሺህ ብር/፣ ለሎት 5-1,500.00 /አንድ ሺህ አምስት መቶ ብር/፣ ለሎት 6 - 6,000.00
/ስድስት ሺህ ብር/፣ ሎት 7 - 5,000.00 /አምስት ሺህ ብር /፣ ለሎት 8 - 5,000.00 /አምስት ሺህ ብር/፣ ሎት 9
- 1,000.00 /አንድ ሺህ ብር/፣ ሎት 10 - 5,000.00 /አምስት ሺህ ብር/፣ ለሎት 11 – 10,000.00 /አስር ሺህ
ብር/፣ ለሎት 12 – 7,500.00 /ሰባት ሺህ አምስት መቶ ብር/ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትእዛዝ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ
የባንክ ዋስትና አለዚያም በመ/ቤታችን የገቢ ደረሰኝ በመ/ሂ 1 ገቢ አድርጎ ሰነዱን አያይዞ ማቅረብ አለበት::
7. ማንኛውም ተጫራች ሃሳቡን ዋናና ቅጂ በማለት ኦሪጅናሉን ለብቻ ኮፒውን ለብቻ በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ
በማድረግ ስሙን፣ ፊርማውንና ማህተሙን በማሳረፍ አነደድ ወረዳ ሲቪል ሰርቪስ ግቢ በሚገኘው ገንዘብ ጽ/ቤት ግዥና ንብረት አስተዳደር
ቡድን ቢሮ ቁጥር 01 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ሰዓት ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀንና እስከ
16ኛው ቀን 3፡30 ሰዓት ድረስ ማስገባት አለበት::
8. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በ16ኛው ቀን በ3፡30 ሰዓት ታሽጎ በ4፡30
ሰዓት ላይ ይከፈታል:: የስራ ቀን ካልሆነም በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል:: ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው
በጨረታ መክፈቻ ሰዓት ባይገኙም መ/ቤቱ ጨረታውን የመክፈት መብት ያለው ሲሆን በጨረታ መክፈቻ ቀንና ሰዓት ያልተገኙ ተወዳዳሪዎች
በተላለፈው ውሳኔ ተገዥ ይሆናሉ::
9. በጨረታ ሰነዱ ላይ የማብራሪያ/ የማሻሻያ ጥያቄን በተመለከተ ጨረታው ከወጣበት ጀምሮ እስከ 10ኛው
ቀን ድረስ ማቅረብ ይቻላል::
10.አሸናፊው አካል ያሸነፈባቸውን እቃዎች ጠቅላላ ወጪውን በመሸፈን አነደድ ወረዳ ግብርና ጽ/ ቤት ድረስ
የማቅረብ ግዴታ ያለባቸው ሆኖ ለሁሉም ሎቶች ለውል መያዣ የሚፈለጉ ወጪዎችን አሸናፊው አካል የሚሸፍን ይሆናል::
11.ግዥ ፈጻሚው አካል ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ሲሆን በጨረታው መሰረዝ
ምክንያት ለወጣው ወጪ ግዥ ፈጻሚው አካል ተጠያቂ አይሆንም::
12.በጨረታ ሂደቱ ቅር የተሰኘ ማንኛውም ተወዳዳሪ የጨረታው አሸናፊ ከተገለጸበት በ5 የስራ ቀናት ውስጥ
አቤቱታ ጨረታውን ላጣው አካል የበላይ ሃላፊ በጽሑፍ ሊያቀርብ ይችላል:: አቤቱታ የቀረበበት መ/ቤትም ምላሹን አቤቱታው በቀረበለት
በ4 የስራ ቀናት ውስጥ በጽሑፍ ለአቤቱታ አቅራቢው መልስ መስጠት አለበት::
13.ውደድሩ የሁሉም ሎቶች በጥቅል ዋጋ ስለሚታይ ተጫራቾች በአንድ ሎት ያሉትን ዝርዝር አቃዎች ሁሉንም
ዋጋ መሙላት ያለባቸው ሲሆን ግዥ ፈጻሚው አካል ካወጣው ስፔስፊኬሽን ውጭ በራሱ ስፔስፊኬሽን የሞላ ተወዳዳሪ ከውድድር ውጭ ይሆናሉ::
14.በውደድሩ አሸናፊ የሆኑ ተወዳዳሪዎች እቃውን ማቅረብ ያለባቸው ውል ከያዙበት ቀን ጀምሮ በሚቆጠር በ20ቀንውስጥ
ማቅረብ ያለባቸው ሲሆንሙያ የሚጠይቁ እቃዎች ደግሞ በሚመለከተው ባለሙያ የሚረጋገጥ ይሆናል::
15.በማንኛውም ግዥ ለእቃዎች ከብር 20,000.00 /ሃያ ሺህ ብር/ በላይ ለአገልግሎት ግዥ ደግሞ ከ10,000.00
/አስር ሺህ ብር/ በላይ ለሚሆኑ ግዥዎች አቅራቢው ከሚፈጸምለት ክፍያ ላይ 3% ቅድመ ግብር /ዊዝ ሆልድ/ ተቀንሶ የሚቀር ሲሆን
በውል አፈጻጸም ወቅት የዋጋ ማስተካከያ ማድረግ አይፈቀድም::
16.ግዥ ፈጻሚው መ/ቤት በወጡት በሁሉም ሎቶች የቅድሚያ ክፍያ የማይሰጥ ሲሆን ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ
ከፈለጉ አነ/ወ/ሲ/ሰ/ጽ/ቤት ውስጥ ከሚገኘው ገንዘብ ጽ/ቤት ግዥና ንብረት አስተዳደር ቡድን ቢሮ ቁጥር 01 በአካል ወይም በስልክ
ቁጥራችን 09-13-27-18-23/ 09-46- 08-84-03 በመደወል ማግኘት ይችላሉ::
በምስራቅ ጉጃም ዞን የአነደድ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ ቤት