አዲስ ዘመን እሁድ ግንቦት 11 ቀን 2016ዓ.ም
ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
በአብክመ ደቡብ ወሎ አስተዳደር ዞን የሐይቅ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት ግዥ፣ ፋይናንስና ንብረት
አስተዳደር ቡድን በ2016 በጀት ዓመት
- ሎት 1፡ በቀበሌ 2 አስተዳደር ክልል ከከበደ እሸቴ እስከ አበሩ ያሲን እና ከሸህ ዑመር ቤት እስከ
ቀበሌ 4 ባጃጅ ተራ ድረስ የጠጠር መንገድ ጥገና ሥራ
- ሎት2 ፤ በቀበሌ 3 አስተዳደር ከልል ከመገንጠያ እስከ ሆስፒታል በር ድረስ የጠጠር መንገድ ጥገና ሥራ
ለማሠራት በግልፅ ጨረታ ማወዳደር ይፈልጋል ፡፡ በዚህም መሠረት፡-
1, በዘመኑ የታደሰ የንግድ ሥራ ፈቃድ እና የብቃት ማረጋገጫ ምሥክር ወረቀት ያላቸው፤
2. እስካቫተር ፣ ግሬደር እና ሮሎ የባለቤትነትን የሚያረጋግጥ ሊብሬ ህጋዊ ሠነድ እና በኪራይ ከሆነ የኪራይ
ዉል ስምምነት ሊብሬ የባለቤትነት ህጋዊ ሠነድ ማያያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡
3 የዕቃ ወይም የአገልግሎት ግዥው መጠን ብር 200,000.00 ( ሁለት መቶ ሺ ብር ) እና በላይ ከሆነ
የተጨማሪ እሴት ታክስ /VAT/ ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
4. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ሲገዙ ለእያንዳንዱ የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 400.00 ( አራት መቶ
ብር ) በመክፈል ሐይቅ ከተማ አስ/ገንዘብ ጽ/ቤት ግዥ፣ ፋይ/ንብ/አስተዳደር ቡድን ቢሮ ቁጥር 4 ድረስ በመቅረብ መግዛት ይችላሉ፡፡
5. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ሎት ፣ በቀበሌ 2 አስተዳደር ክልል ከከበደ እሸቴ እስከ አበሩ
ያሲን እና ከሸህ ዑመር ቤት እስከ ቀበሌ 4 ባጃጅ ተራ ድረስ የጠጠር መንገድ ጥገና ሥራ ብር 20,382.08፣ ሎት2 በቀበሌ
3 አስተዳደር ክልል ከመገንጠያ እስከ ሆስፒታል በር ድረስ የጠጠር መንገድ ጥገና ሥራ ብር 38,977.7 በባንክ በተረጋገጠ ትዕዛዝ
( CPO) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በባንክ የተረጋገጠ ቢድ ቦንድ ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
6. የጨረታ ሰነዱን ዋናና ቅጅ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ሐይቅ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት
ግዥ ፋይ/ንብ/አስተዳደር ቡድን ቢሮ ቁጥር 14 ጋዜጣው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 21 ቀናት ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
7. ጨረታው በ22ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ታሽጎ 4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው
በተገኙበት ይከፈታል ( ባይገኙም ይከፈታል ) ቅዳሜና ዕሁድ ወይም የሕዝብ በዓል ቀን ከሆነ በቀጣዩ የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት
ይፈፀማል፡፡
8. ማንኛውም ተጫራች ጨረታው ከተከፈተ በኋላ ራሱን ከጨረታው ውድድር ማግለል የማይችል ሲሆን፤ በጨረታ
ሠነዱ የሠጠውን ዋጋና መግለጫ መለወጥና ማሻሻል አይችልም፡፡
9. የሂሣብ ስሌት ( አርቲሜቲክ ቼክ ) በግዥ ፈፃሚው መ/ቤት ባለሙያ ከሚስተካከለው ዉጭ በተጫራቾች የሚቀርበው
የመጫረቻ ሠነድ ላይ በነጠላና ጠቅላላ ዋጋ ላይ ስርዝ ድልዝ ካለ ተጫራቹ ከጨረታ ዉጭ ይሆናል፡፡
10. ተጫራቾች ለሥራው የሚያስፈልጉ ማሽነሪዎችንና የሰው ኃይልን በሙሉ ራሣቸውን ችለው ነዉ፡፡
11 ተጫራቾች ደረጃ 7 እና ከዚያ በላይ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡ ጠቅላላ ሥራ ተቋራጭ ፈቃድ ያላቸው፤
12. መንገድ ሥራ ተቋራጭ ፈቃድ ያላቸው፤ አሸናፊው የሚለየው በሎት ጠቅላላ ዋጋ ድምር ዉጤት ነው፡፡
13. የሚቀርቡ መረጃዎች ግልፅና ጎላ ብለዉ የሚነበቡ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
14. ጽ/ቤቱ እንደ በጀቱ ሁኔታ በጨረታ ሰነዱ ላይ የተዘረዘሩትን ሥራዎች ብዛት 20 % መጨመርም ሆነ
መቀነስ ይችላል፡፡
15. የሚሠሩት የጠጠር መንገድ ጥገና ሥራዎች ጥራታቸው የተጠበቀ መሆን አለበት ፡፡
16. መ/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
17. ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 033 222 01 62 ደውሎ መጠየቅ ይችላል ::
በደቡብ ወሎ ዞን የሐይቅ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት የግዥ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር
ቡድን